የአድዋ ድል በ"አንቺሆዬ ለኔ" ይህ የሙዚቃ ቅንብር የኢትዮጵያን የነፃነት ተምሳሌት የሆነውን የአድዋን ድል በሀገረሰባዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ቅኝት በዝርዝር የሚተርክ የጥበብ ሥራ ነው። በመክፈቻ፦ ሥራው የሚጀምረው በከፍተኛው የአድዋ ተራሮች ላይ በሚሰማ፣ ልብ የሚነካና የጀግናን የጦርነት ውሎ በሚያወሳ ድምፅ ነው። ለዚህም ጥንታዊውን የአንቺሆዬ ቅኝት ይዟል። የጀግንነት ስሜት ባለው ምትና የትዝታ ወኔን በሚቀሰቅስ ድምፅ ፣ እንደ ተጓዥ ተዋጊዎች የእግር ኮቴና እንደ ጦር ግንባር ነጋሪት በየመሃሉ ያስተጋባል። በሙዚቃው ውስጥ የሚሰሙት የሩቅ የፈረሶች ኮቴ፣ የጀግኖች ፉከራና ሽለላ፣ እንዲሁም የጦር መሣሪያዎች መጋጨት ሙዚቃው ወደ ጦርነቱ ድባብ ወስዶን እንዲያቆየን ያደርጉታል። የኢትዮጵያን ድልና ሉዓላዊነት በዚህ ሙሲዝቃ። ይምረጡን! Source Link Link