በድጋሜ እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሰን! እኛ ጥቁር ህዝቦች ይሄን የማይደበዝዝ ደማቅ አኩሪ የድል በዓል ሁሌም ስንዘክረው፣ ስንማርበትና ወደ ህልማችን ለምናደርገው ጉዞ ስንነሳሳበት እንኖራለን። በዚህ የኤ.አይ ሙዚቃ 2 ወንድና ሴት አቀንቃኞች በመቀባበል የሚያቀርቡት ሲሆን የቢቱ ንሸጣ የነጋሪት ጉሰማ ነው። በዚህ ሙዚቃም አድዋ ቀለማችን ፣ መገለጫችን ፣ የክብር መጠሪያ ስማችን ፣ የመላው ጥቁር ህዝብ ድል አርማ እንደሆነ እያዜሙ ጥቁር ህዝብ ነጭን ድል አድርጎ ከዛም ድል ያደረጋቸውን ምርኮኞችን በሰላም ወደ ሀገራቸው ሸኝቶ የሰዎችን እኩልነትና የሰውነትን ክብር በአድዋ ድል ዕለት ለአለም ህዝብ እንዳሳየ እኛም ጠንክረን ሰርተን አንገት ያስደፋንን ድህነት ካሸነፍን ያ! ድላችን የዘመናችን አድዋ እንደሚሆን ያቀነቅናሉ። https://suno.com/s/ljQijKlSUwnjEG9P